Quantcast
Channel: , Author at Satenaw: Ethiopian News | Breaking News: Your right to know!
Viewing all articles
Browse latest Browse all 8076

በመተከል ዞን በዜጎች ላይ ጥቃት በፈፀሙ ታጣቂዎች ላይ በተወሰደው እርምጃ በርካቶች መደምሰሳቸውን ተገለጸ

$
0
0

አዲስ አበባ ፣ ጥር 7 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በመተከል ዞን በዜጎች ላይ ጥቃት በፈፀሙ ታጣቂዎች ላይ በተወሰደው እርምጃ በርካቶች መደምሰሳቸውን በፌዴራል መንግስት የተቋቋመው የተቀናጀ ግብረ ሃይል አስታወቀ።

በዞኑ ሁሉም ወረዳዎችና ቀበሌዎች የሰዓት እላፊ ገደብ መጣሉም ተገልጿል።

በፌዴራል መንግስት የተቋቋመው የተቀናጀ ግብረ ሃይል አባል ብርጋዴል ጄነራል አለማየሁ ወልዴ ለኢዜአ እንደገለጹት በመተከል ዞን በዜጎች ላይ ጥቃት በፈፀሙ ታጣቂዎች ላይ በተወሰደው እርምጃ በርካቶች ሲደመሰሱ ከፊሎቹ ተማርከዋል።

ያመለጡ የታጣቂ ቡድኑን አባላት የማደን ስራም ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።

ከሁለት ቀን በፊት በዞኑ የኦነግ ሸኔና የህወሃት ተላላኪ ታጣቂ ቡድን አባላት በፈጸሙት ጥቃት የ74 ንጹሃን ዜጎች ህይወት ማለፉን ብርጋዴል ጄነራል አለማየሁ ገልጸዋል።

ግብረ ሃይሉ የታጣቂውን የሽፍታ ቡድን እንቅስቃሴ በመከታተል የተቀናጀ የህግ ማስከበር እርምጃ በማካሄድ ላይ እንደሚገኝ እና በዚህም በርካታ የታጣቂ ቡድኑ አባላት መደምሰሳቸውን ጠቅሰዋል።

የታጣቂ ሃይሉን አባላት በማደን ተግባር የፀጥታ ሃይሉ ከህዝቡ ጋር በመተባበር ጠንካራ ስራዎችን በማከናወን ላይ መሆናቸውንም ተናግረዋል።

በንፁሃን ዜጎች ላይ በተፈፀመው አረመኔያዊ ድርጊት ግብረ ሃይሉ የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን ገልጾ፤ ግብረ ሃይሉ ይህንን እኩይ አላማ አንግቦ የሚንቀሳቀሰውን ታጣቂ ቡድን ሙሉ ለሙሉ በመደምሰስ የአካባቢውን ሰላም ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ መሆኑን አረጋግጠዋል።

ብርጋዴል ጄነራል አለማየሁ እንዳሉት ከትናንት ጀምሮ በዞኑ ሁሉም ወረዳዎችና ቀበሌዎች የሰዓት እላፊ ገደብ ተጥሏል።

በዚህም ከምሽቱ 1 ሰዓት ጀምሮ እስከ ጠዋቱ 12 ሰዓት ድረስ በአካባቢው ምንም አይነት እንቅስቃሴ ማድረግ አይፈቀድም።

ይህንን ገደብ ተላልፎ የሚገኝ እግረኛም ሆነ ተሽከርካሪ ካለ እርምጃ የሚወሰድበት መሆኑ ታውቋል።

በታጣቂ ሃይሉ ላይ እየተወሰደ ያለውን እርምጃና ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የሚደረገውን ጥረት ባልተገባ መንገድ የሚገልጹ አካላትም ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ማሳሰባቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Source link

The post በመተከል ዞን በዜጎች ላይ ጥቃት በፈፀሙ ታጣቂዎች ላይ በተወሰደው እርምጃ በርካቶች መደምሰሳቸውን ተገለጸ appeared first on Satenaw Ethiopian News/Breaking News.


Viewing all articles
Browse latest Browse all 8076

Trending Articles