Quantcast
Channel: , Author at Satenaw: Ethiopian News | Breaking News: Your right to know!
Viewing all articles
Browse latest Browse all 8076

የከተራና የጥምቀት በዓላት በሰላም እንዲከበሩ ዝግጅት ተጠናቆ ወደ ስራ ተገብቷል- የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን

$
0
0

አዲስ አበባ ፣ ጥር 7 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የዘንድሮው የከተራና የጥምቀት በዓላት በሰላም እንዲከበሩ ዝግጅቱን አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

ህብረተሰቡ ለፀጥታ ስራው ስኬታማነት እያደረገ ያለውን ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥልም ኮሚሽኑ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡

ኮሚሽኑ በዓላቱ በሰላም ተጀምረው እንዲጠናቀቁ ለወንጀል እና ትራፊክ አደጋ መከላከል ተግባሩ ልዩ ትኩረት በመስጠት በርካታ የሰው ኃይል ማሰማራቱን ገልፆ በታቦት ማደሪያ ስፍራዎች በተለይም በርካታ የበዓሉ ታዳሚዎች በሚገኙበት ጃን ሜዳ ጊዜያዊ ፖሊስ ጣቢያ ተከፍቶ አግልጋሎት እንደሚሰጥም ተገልጿል፡፡

ኮሚሽኑ ከበዓሉ መንፈስና ከህገ-መንግስቱ እንዲሁም ከህግ ጋር የሚቃረኑ የሌላን ወገን መብት የሚጋፉ መልዕክቶችም ሆኑ ድርጊቶች ፍፁም ተቀባይነት እንደሌላቸውና ይህን ሲፈፅሙ በሚገኙ ላይ በህግ አግባብ እርምጃ እንደሚወስድም አስታውቋል፡፡

ርችት መተኮስ ለፀረ-ሰላም ኃይሎች ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር በመሆኑም ርችት መተኮስ ፍፁም የተከለከለ መሆኑን ገልጿል፡፡

በዓሉ በሚከበርበት ስፍራ ምንም አይነት የጦር መሳሪያ፣ ተቀጣጣይም ሆነ ስለት ነገሮችን ይዞ መንቀሳቀስ ክልክል እንደሆነ የበዓሉ ታዳሚዎች ተገንዝበው ለፍተሻ ትብብር እንዲያደርጉ እንዲሁም በዓሉ በሰላም እንዳይከበር አንዳንድ ፀረ-ሰላም ኃይሎች የብሔር ግጭት ለማስነሳት እንደሚንቀሳቀሱ ህብረተሰቡ ተገንዝቦ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስቧል፡፡

ታቦታት በሚያልፉበት ወቅትም አሽከርካሪዎች የፀጥታ አካላት ለሚሰጧቸው ተዕዛዝ የተለመደ ትብብራቸውን እንዲያደርጉ ኮሚሽኑ ጥሪው አቅርቧል፡፡

ህብረተሰቡ በማንኛው ወቅት ከፀጥታ ስራ ጋር ተያያዥ እና አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙትም ይሁን ጥቆማ ለመስጠት እንዲሁም የፖሊስ አገልግሎትን ለማግኘት በስልክ ቁጥር 01-11-26-43-77 ፣ 01-11-26-43-59 ፣ 01-18-27-41-51 ፣ 01-11-11-01-11 እና በ991 ነፃ የስልክ መስመር መጠቀም ይቻላልም ነው ያለው፡፡

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Source link

The post የከተራና የጥምቀት በዓላት በሰላም እንዲከበሩ ዝግጅት ተጠናቆ ወደ ስራ ተገብቷል- የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን appeared first on Satenaw Ethiopian News/Breaking News.


Viewing all articles
Browse latest Browse all 8076

Trending Articles